የልደት በዓልን ከተማሪዎች2018

የመቐለ ዩኒቨርሲቲ ከፍተኛ አመራሮች የልደት በዓልን ከተማሪዎች ጋር በድምቀት አከበሩ
​የመቐለ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች የኢየሱስ ክርስቶስን የልደት በዓል (ገና) በዛሬው ዕለት በሁሉም የዩኒቨርሲቲያችን ግቢዎች በድምቀት አክብረዋል፡፡
​በዓሉን ምክንያት በማድረግ የዩኒቨርሲትያችን የአስተዳደርና ልማት ምክትል ፕሬዚዳንት ዶ/ር ተከስተ ብርሃኑን ጨምሮ ሌሎች ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች (የማኔጅመንት አባላት) በግቢዎቹ በመዘዋወር ከተማሪዎች ጋር ምሳ ተጋርተዋል።

የልደት በዓልን ከተማሪዎች2018
​ዶ/ር ተከስተ በዓሉን አስመልክተው ባስተላለፉት መልእክት፤ በዓሉ ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች የሰላምና የፍቅር እንዲሆን ተመኝተዋል፡፡ አክለውም በዓሉ በተማሪዎች ዘንድ እንዲህ ደምቆ እንዲከበር አስተዋጽኦ ላደረጉ አካላት ምስጋና አቅርበዋል።

Related Articles