የፋሲካ በዓል አከባበር በመቐለ ዩኒቨርሲቲ
የመቐለ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች የፋሲካን በዓል ከዩኒቨርሲቲው ከፍተኛ ማናጀመንት አባላት ጋር በጋራ አክብረዋል።
በአከባበሩ ላይ የተገኙት የዩኒቨርሲቲው አመራሮች ለተማሪዎቹ የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት ያስተላለፉ ሲሆን፣ በዓሉ የሰላም፣ የፍቅርና የአንድነት እንዲሆን ተመኝተዋል። ተማሪዎቹም በበኩላቸው አመራሮቹ ከጎናቸው በመገኘታቸው የተሰማቸውን ደስታ ገልጸዋል።
ይህ መሰል መርሃ-ግብር በዩኒቨርሲቲው ማህበረሰብ መካከል ያለውን ቤተሰባዊ ትስስር ይበልጥ የሚያጠናክር ነው።
መልካም የፋሲካ በዓል!
