የመቐለ ዩኒቨርሲቲ ደማቅ የምርቃት ስነ-ስርዓት!
የመቐለ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ዶ/ር ፋና ሓጎስ ለተመራቂ ተማሪዎች እና ለቤተሰቦቻቸው የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል። በዘንድሮው የምርቃት ስነ-ስርዓት ለስኬት የበቁ ተማሪዎች ዝርዝር መረጃ እንደሚከተለው ቀርቧል፡
ጠቅላላ ተመራቂዎች፡ 2,931
(ከነዚህም ውስጥ 849ቱ ሴት ተመራቂዎች ናቸው)
ዝርዝር መረጃ፡
የመጀመሪያ ዲግሪ፡ 1,864 ተመራቂዎች
ማስተርስ ዲግሪ፡ 939 ተመራቂዎች (45 ዓለም አቀፍ ተማሪዎችን ጨምሮ)
ስፔሻሊቲ፡ 83 ተመራቂዎች
ዶክትሬት ዲግሪ (PhD)፡ 45 ተመራቂዎች
"ይህ እጅግ አስደሳች ወቅት ነው። ለተመራቂዎቻችን እና ለቤተሰቦቻችሁ በድጋሚ እንኳን ደስ አላችሁ እላለሁ።"
ዶ/ር ፋና ሓጎስ (የመቐለ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት)
እንኳን ደስ አላችሁ!