
ማስታወቂያ
ጉዳዩ፡- የብሄራዊ ድህረ-ምረቃ (NGAT) መግቢያ ፈተና ቀንን ስለማሳወቅ
በ2017 ዓ.ም የሶስተኛ ዙር የNGAT አመልካቾች ምዘገባ ተጠናቅቋል፡፡ በዚሁ መሰረት ለመፈተን ያመለከታችሁ አመልካቾች ፈተናው የሚሰጠው ዓርብ መጋቢት 5 ቀን 2017 ዓ.ም ከጠዋቱ 3፡00 ጀምሮ መሆኑን አውቃችሁ በተጠቀሰው ቀንና ሰዓት በምትመደቡበት የፈተና ማዕከላት እንድትገኙ እናሳውቃለን፡፡
የሶስተኛው ዙር (3rd Round) የ2017 ዓ.ም የድህረምረቃ ፕሮግራሞች የመግቢያ ፈተና (NGAT) የምዝገባ እና የፈተና ጊዜን ስለማሳወቅ
.
ሀገር አቀፍ የድኅረ-ምረቃ ፕሮግራሞች የመግቢያ ፈተና (NGAT) አመልካቾች ምዝገባ ከየካቲት 27 እስከ መጋቢት 1/2017 ዓ.ም ማታ 12፡00 ሰዓት ድረሰ ብቻ በ https://ngat.ethernet.edu.et/registration የመመዝገቢያሊንክ በኩል ይከናወናል፡፡
ከምዝገባው ጋር ለተያያዘ ማንኛውም ጥያቄ በሥራ ሰዓት በኢሜል አድራሻ This email address is being protected from spambots. You need JavaScript enabled to view it. ወይም በስልክ ቁጥር 0920157474 (Enatnesh Gebeyehu) እና 0911335683 (Fasil Tsegaye) ማብራሪያ መጠየቅ ይቻላል።
.
የመፈተኛ ' USER NAME ' እና " PASSWORD ' በመመዝገቢያ ፖርታል በኩል የሚላክ ሲሆን፤ የመመዝገቢያ ክፍያ ብር 750 በቴሌብር በኩል ብቻ መፈጸም ይጠበቅባችኋል፡፡
.
ማሳሰቢያ
ፈተናው የሚሰጥበት ቀን በቀጣይ የምናሳውቅ ሆኖ በፈተና ወቅት የተሰጣችሁን User Name and Password፣ እና ማንነታችሁን የሚገልጽ መታዋቂያ ይዛችሁ መቅረብ ይጠበቃባችኋል።
የኢፌድሪ ትምህርት ሚኒስቴር
Contact US
Mekelle University
Corporate Communication Directorate office
Email: ccia@mu.edu.et
Phone: +251 344 40 40 05
website: www.mu.edu.et
Facebook: @MekelleUniversity
Twitter: @MekUniETH
