
መቐለ ዩኒቨርሲቲ የህፀተ ዝናብ ግብርናና ተፈጥሮ ሃብት ኮሌጅ ለ500 የእንደርታ ወረዳ አርሶ አደሮች የ**"ቁንጮ"** ጤፍ ምርጥ ዘር ማከፋፈሉን አስታወቀ። የዘር ስርጭቱ ዛሬ ሓምሌ 13/2018 ዓ.ም በመቐለ ዩኒቨርሲቲ ዋና ግቢ ተካሂዷል።
ዩኒቨርሲቲው እንደወትረው ሁሉ አሁን ባለው ውስን በጀት ቢሆንም ለህብረተሰቡ የሚሰጠውን የማህበረሰብ አገልግሎት አጠናክሮ እንደሚቀጥልም ተገልጿል።
ከመርሃ ግብሩ የተደመጡ ዋና ዋና ነጥቦች፡

ዶ/ር ገብረሐዋርያ በሪሁ (የመቐለ ዩኒቨርሲቲ የማህበረሰብ አገልግሎት እና ኢንዱስትሪ ትስስር ዳይሬክተር)፡
የማህበረሰብ አገልግሎት የዩኒቨርሲቲው አንዱና ዋነኛው ተልዕኮ መሆኑን ጠቅሰው፣ አርሶ አደሩን የመደገፉ ስራ በዚሁ እንደማይበቃና በቀጣይም ተመሳሳይ እገዛ እንደሚደረግ ገልጸዋል።
ተባባሪ ፕሮፌሰር አለሙ አርአያ (የህፀተ ዝናብ ግብርናና ተፈጥሮ ሃብት ኮሌጅ ምክትል ዲን)፡
ይህ የኮሌጁ እገዛ ለ3ኛ ጊዜ የተካሄደ መሆኑን ጠቁመው፣ በዚህ ዙር ለአንድ አርሶ አደር 15 ኪሎ ግራም ምርጥ ዘር መሰጠቱን አብራርተዋል።
ዶ/ር ወንድም ይግዛው (የእፅዋትና ፍራፍሬ ሳይንስ ትምህርት ክፍል ሀላፊ)፡
ተጠቃሚ አርሶ አደሮች ዘሩን በተገቢው መንገድ ተክለው የተሻለ ምርት እንዲያገኙ የሚያስችላቸውን ሙያዊ ማብራሪያና ምክር ሰጥተዋል።
